ሙሽሮች በወዳጅነት ፓርክ የሠርግ አጸድ

Your browser doesn’t support HTML5

በአዲስ አበባ የተዘጋጀው አዲሱ ምዕራፍ ሁለት የወዳጅነት ፓርክ ወደ 50 የሚጠጉ ጥንዶችን የሠርግ ሥነ ስርዓት በማስተናገድ ትናንት ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡

ለሠርግ ሥነ ስርዓት የሚሆን “የሠርግ አጸድ” የተባለ ሥፍራን አካቶ በተገነባው በዚህ ፓርክ በተካሔደው የሠርግ ሥነ ስርዓት ላይ የተሞሸሩ ጥንዶች፣ በዚህ መልኩ የሠርግ ድግስ ማድረግ ከወጪ እንዲሁም ትውውቅ ከመፍጠር አንጻር አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም መበረታታት አለበት ይላሉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በስፍራው ተገኝተው ከሙሽሮቹ ጋር በጋራ ኬክ ቆርሰዋል፡፡