የተሰናባቹ 2014 ግምገማ እና የአዲሱ ዓመት ምኞት - ከነዋሪዎች አንደበት

Your browser doesn’t support HTML5

እየተገባደደ ያለው የ2014 ዓ/ም በተለይ ከሠላምና ጸጥታ ጉዳዮች አንጻር አስቸጋሪ እንደነበር የገለፁት የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ኢትዮጵያዊያን ዕሁድ የሚጀምረው አዲስ ዓመት የተሻለ እንደሚሆን ተስፋቸውን ገልጸዋል።

አዲሱ የ2015 ዓ/ም የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ሰላማዊ እልባት የሚያገኝበት እንዲሆን ምኞታቸውን ያንጸባረቁም አሉ።

ሌሎች ደግሞ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥም ቢሆን ተሳኩ ያሏቸውን የሕዳሴውን ግድብ ሙሌት የመሳሰሉ ክንውኖች በአዎንታዊነት ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያዊያን አዲሱን የ2015 ዓ/ም ለመቀበል እየተዘጋጁ ባሉበት በዚህ ሳምንት የአሮጌውን የ2014 ግምገማቸውን እና ለ2015 ያላቸውን ምኞታቸውን መጠየቃችንን ቀጥለናል።