ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገለፀ

Your browser doesn’t support HTML5

ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገለፀ

ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ኢትዮጵያ ውስጥ ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ልዩ ልዩ ድጋፎች እያበረከተ መሆኑን አስታወቀ።

ለአብነትም በዚህ ሳምንት 5ኛውን ዙር መድሃኒት፣ ምግብና ቁሳቁሶች የጫኑ የእርዳታ ተሽከርካሪዎች ትግራይ መግባታቸውን አስታውቋል።

በአፋር፣ አማራና ኦሮምያ ክልልም ልዩ ልዩ ድጋፎችን እያበረከቱ መሆኑን ገልፆ በቀጣይ የዘር ወቅት በመሆኑ በግብርናው ዘርፍ ላይ ያተኮረ ድጋፍ ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታውቋል።