ጠ/ሚ ዐቢይ ለአፍሪካ ህብረት ልኡካን ቡድን ማብራሪያ ሰጡ

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያ ሕግን ለማስከበርና የህወሓትን “ወንጀለኛ ቡድን” ለሕግ ለማቅረብ የምታደርገውን ጥረት የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር የሚረዱት በመሆናቸው ያላቸውን ምስጋና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ። ሕግ የማስከበሩን ሂደትም ለሊቀ መንበሩ ልዩ ልኡካን ቡድን ማብራሪያ ሰጥተዋል።