የማኅበራዊ መገናኛ አንቂና ፀሃፊ ታሰሩ

Your browser doesn’t support HTML5

በማኅበራዊ ሚድያ ላይ በአንቂነትና መንግሥትን በመቃወም የሚታወቀው እያስፔድ ተስፋዬ በአዲስ አበባ ፖሊስ ተይዞ መታሰሩ ታውቋል። በሌላ በኩል ደግሞ ደራሲና ተርጓሚ ህንሴኔ መኩሪያም ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በአዲስ አበባ ፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ጓደኛቸውና የሥራ ባልደረባቸው ለቪኦኤ ገልፀዋል።