የቡና ዲፕሎማሲ

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያውያን አንኳር ባህል እና የማኅበራዊ ሕይወት ማድመቂያ የኾነው የቡና አፈላል ሥነ ሥርዐት በ38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ መሰብሰቢያ አዳራሽ ለእንግዶች መስተናገጃ ቀርቧል። ከጉባኤው ጎን ለጎን የኢትዮጵያ ባህል እና ቱሪዝም ሀብቶችን ለተሳታፊዎች የማስተዋወቅ ሥራ እየተከናወነ መኾኑንም የቱሪዝም ሚኒስትር ድኤታ ዶር. እንደገና አበበ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡