የትራምፕ ሁለተኛ የሥልጣን ዘመን ለአፍሪካ ምን ሊመስል ይችላል?
Your browser doesn’t support HTML5
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ሥልጣን እየተመለሱ ባሉበት ወቅት ከአፍሪካ ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት በተለይ ከፀጥታ እና ደህንነት ትብብር አንፃር ምን ሊመስል ይችላል የሚለው ጥያቄ ጎልቶ ይነሳል። አፍሪካ ለአሜሪካ ቀዳሚ የፖለቲካ፣ የደህንነት እና የስትራቴጂ አቅጣጫ አለመሆኗን የሚገልጹት የአፍሪካ ጉዳይ ተንታኞች፣ ትራምፕ በአፍሪካ ላይ ያላቸው ትኩረት እንደ ሩሲያ እና ቻይና ያሉ ሀያል ሀገራትን በመገዳደር ላይ የተመሰረተ ሊሆን እንደሚችል አመልክተዋል።