“እውነተኛ ሠላም፣ የግጭት አለመኖር ብቻ አይደለም” የዩናይትድ ኤምባሲ ምክትል ኃላፊ

Your browser doesn’t support HTML5

“እውነተኛ ሠላም፣ ግጭት እንዲቆም ማድረግ ብቻ ሳይሆን፣ የፍትህ፣ የውይይት እና የጋራ መከባበር መኖር ነው” ሲሉ፣ በኢትዮጵያ ዩናይትድ ስቴት ኤምባሲ ምክትል ኃላፊ ግዌንዶሊን ግሪን ተናግረዋል።

ምክትል ኃላፊዋ ይህን የተናገሩት ባለፈው ቅዳሜ መስከረም 11 ቀን 2017 ዓ/ም በድሬዳዋ በተከበረው የዓለም የሠላም ቀን አከባበር ላይ በተገኙበት ወቅት ነው፡፡ እለቱን አስመልክቶ በተዘጋጀው የእግር ጉዞ ላይም ተሳትፈዋል።