ካማላ ሐሪስ እና ዶናልድ ትረምፕ በኢሚግሬሽን ጉዳይ

Your browser doesn’t support HTML5

በመጪው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ መራጮች ከፍተኛ ትኩረት ከሚሰጧቸው ጉዳዮች አንዱ የኢሚግሬሽን ጉዳይ መሆኑ ይታወቃል። ምክትል ፕሬዝደንት ካማላ ሐሪስ አቃቤ ሕግ ሆነው በሠሩባቸው ጊዜያት ስላከናወኗቸው ሥራዎች በማውሳት የምረጡኝ ዘመቻቸውን እያካሄዱ ናቸው፡፡

የቀድሞ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ በበኩላቸው የባይደን ሐሪስ አስተዳደርን ሬኮርድ በመተቸት ህጋዊ ፈቃድ የሌላቸውን ፍልሰተኞች በብዛት እንደሚያስወጡም ቃል በመግባት ላይ ናቸው።

በአሊን ባኾስ የተጠናቀረውን ዘገባ ቆንጅት ታየ ወደ አማርኛ መልሳዋለች፡፡