75ኛ ዓመቱን የሚያከብረው ኔቶ በዋሽንግተን ጉባኤ ያደርጋል

Your browser doesn’t support HTML5

የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) በመጪው ሳምንት ዋሽንግተን ዲሲ ላይ በሚያደርገው ጉባኤ፣ ዩክሬንን አባል የማድረጉን ሂደት ለማፋጠን ተጨባጥ ያላቸውን እርምጃዎች ይፋ ያደርጋል ተብሏል።

ጉባኤው በተጨማሪም፣ ሩሲያ በዩክሬን ላይ ጦርነት በማካሄድ ላይ ባለችበት በዚህ ወቅት የሚታዩትን አንገብጋቢ የፀጥታ ስጋቶችን እንዲሁም በኢንዶ ፓሲፊክ ቀጠና የሚታዩ ስጋቶችን በተመለተ ይወያያል።

የቪኦኤዋ ናይኪ ቺንግ የላከችው ዘገባ እንደሚከተለው ይቀርባል።