በሦስተኛው "የሀጫሉ ሁንዴሳ" ሽልማት ለድምፃዊው ግድያ ፍትሕ ተጠየቀ

Your browser doesn’t support HTML5

ሦስተኛው “የሀጫሉ ሁንዴሳ” ሽልማት፣ ቅዳሜ ምሽት፣ በዐዲስ አበባ ተካሒዷል።

ለታዋቂው ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ መታሰቢያ እንደኾነና የአፋን ኦሮሞ ሥነ ጥበብን የማሳደግ ዓላማ እንዳለው በተገለጸው ሽልማት፣ በተለያዩ ዘርፎች ተወዳድረው ያሸነፉ ድምፃውያንና የሙዚቃ ባለሞያዎች ተሸላሚ ኾነዋል።

የድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ባሌበት እና የሀጫሉ ሁንዴሳ ፋዉንዴሽን ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ፋንቱ ደምሴ፣ “አሁንም ለአርቲስቱ ሞት እውነተኛ ፍትሕ ይሰጥ፤” ሲሉ ጠይቀዋል።