የፀለምቲ ወረዳ ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው እየተመለሱ ናቸው

Your browser doesn’t support HTML5

የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች፣ ከዐማራ ክልል ጋራ የይገባኛል ጥያቄ ከሚነሣባቸው አዋሳኝ አካባቢዎች አንዱ ወደኾነው ፀለምቲ ወረዳ፣ ትላንት ቅዳሜ መመለስ ጀምረዋል፡፡ ትላንት ወደ ወረዳዋ አራት ቀበሌዎች ተፈናቃዮች መመለሳቸው ሲገለጽ፣ የወረዳዋን ከተማ ማይፀብሪን ጨምሮ የስድስት ቀበሌዎች ተፈናቃዮች ዛሬ እና ነገ ይመለሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።