ደሴን የጎበኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከታጣቂዎች ጋራ ለመነጋገር ዝግጁነታቸውን ገለጹ

Your browser doesn’t support HTML5

በዐማራ ክልል የትጥቅ ግጭት በቀጠለበት ኹኔታ ውስጥ ወደ ክልሉ የተጓዙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ትጥቅ ያነገቡ አካላት ወደ ሰላም እንዲመለሱ፥ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች እና ወላጆች የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።