በአማራ ክልል በግጭት አካባቢዎች ያሉ አርሶ አደሮች የእርሻ ሥራቸው መታጎሉን ገለጹ

Your browser doesn’t support HTML5

በአማራ ክልል፣ በመንግሥት እና በፋኖ ቡድን ታጣቂዎች መካከል የቀጠለው ግጭት፣ በወቅቱ የእርሻ ሥራቸው ላይ ዕንቅፋት መፍጠሩን የተለያዩ አካባቢዎች አርሶ አደሮች አመልክተዋል፡፡

ግጭቶች የቀጠሉባቸው የምሥራቅ እና የምዕራብ ጎጃም ዞኖች ውስጥ ያሉ ቀበሌዎች አርሶ አደሮች፣ በቂ የአፈር ማዳበሪያም እያገኙ እንዳልኾነ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡

የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አምሳሉ ጎባው ደግሞ፣ ዘንድሮ ከ5ነጥብ8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ክልሉ በወቅቱ መግባቱን ጠቅሰው፣ ከእዚኽም ውስጥ ከ4ነጥብ9 ሚሊየን በላይ ኩንታል ለአርሶ አደሩ ተሰራጭቷል፤ ብለዋል፡፡