እስራኤል ሔዝቦላን በዲፕሎማሲ እንድትታገል ዩናይትድ ስቴትስ ጥሪ አቀረበች

Your browser doesn’t support HTML5

ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ፣ በዋሽንግተን፣ ከእስራኤል አቻቸው ጋራ የተወያዩት የዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚኒስትር ሎይድ ኦስተን፣ ዮአቭ ጋላንት ሔዝቦላን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲታገሉት ጠይቀዋቸዋል፡፡

የመከላለያ ሚኒስትር ጋላንት፣ ከትላንቱ ውይይት ቀደም ብሎ ሰኞ ዕለት ያወያዩዋቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን ደግሞ፣ በጋዛ ውስጥ ከሐማስ ጋራ የሚካሔደው ጦርነት እንዳይስፋፋ እንዲከላከሉ አሳስበዋቸዋል፡፡

የአሜሪካ ድምፅዋ የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ዘጋቢ ካትሪን ጂፕሰን ያጠናቀረችውን ከተያይዘው ፋይል ያዳምጡ።