በኬንያ የተፋፋመው የወጣቶች የታክስ ሕግ ተቃውሞ ቀጣናዊ አንድም

Your browser doesn’t support HTML5

የአገሪቱ መንግሥት ያወጣውን የታክስ ሕግ ተከትሎ፣ ባለፈው ሳምንት በናይሮቢ ተጀምሮ በመላ አገሪቱ በተስፋፋው የተቃውሞ ሰልፍ፣ ወጣቶች ከፖሊስ ጋራ ተጋጭተው የሰው ሕይወት አልፏል፡፡

የአፍሪካ ቀንድ እና መካከለኛው ምሥራቅ ጉዳዮች ከፍተኛ ተመራማሪው ዶክተር በለጠ በላቸው፣ በአገሪቱ እንዲህ ዐይነት ተቃውሞዎች የተለመዱ እንደኾኑና በመጨረሻ ላይ በምክክር እንደሚፈቱ ይናገራሉ፡፡ ተቃውሞው ከቁጥጥር ውጭ ከኾነ ግን፣ መረጋጋት በራቀው የአፍሪካ ቀንድ ላይ ሌላ ስጋት የሚጨምር ነው፤ ይላሉ፡፡

ኑሯቸውን በናይሮቢ ያደረጉት ኢትዮጵያዊው አቶ ገመቺሳ በፈቃዱ በበኩላቸው፣ አሁን ኹኔታው እየተረጋጋ መምጣቱን ገልጸው፣ ትላንት አይሎ በነበረው ተቃውሞ በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩም እንዳልሰሙ አመልክተዋል፡፡