በጋምቤላ ከተማ ግጭት ሁለት ሰዎች በታጣቂዎች መገደላቸው ተገለጸ

Your browser doesn’t support HTML5

በጋምቤላ ከተማ፣ ባለፈው ሳምንት እሑድ ምሽት በጀመረውና በማግስቱ ሰኞም በቀጠለው ግጭት፣ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

የክልላዊ መንግሥቱ የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ በበኩሉ፣ በግጭቱ ሁለት ሰዎች መገደላቸውንና አራት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ለአሜሪካ ድምፅ አስታውቋል፡፡

በጋምቤላ ከተማ የሚገኙ የመጀመሪያ ደረጃ እና የሪፈራል ሆስፒታሎችም፣ በግጭቱ የቆሰሉ ሰዎችን እያከሙ እንደሚገኙና የሞቱም መኖራቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።