የናይል ወንዝ በውድቅዳቂ ቆሻሻ ተሞልቷል

Your browser doesn’t support HTML5

በአህጉሪቱ ረዥሙ መሆኑ የሚነገርለት እና አሥራ አንድ አገሮችን አቋርጦ የሚፈሰው የናይል ወንዝ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ቁጥሩ ከ200 ሚሊዮን በላይ ለሚደርስ ሕዝብ ዘላቂ የሕይወት ዋስትና ይሰጣል። ይሁን እንጂ ከወንዙ የላይኛው ተፋሰስ አካባቢዎች የሚታየው እና እያደርም እየጨመረ የመጣው የሰዎች እንቅስቃሴ የወንዙን ሥነ-ምህዳር ለአደጋ ማጋለጡ ተዘግቧል።

ሺላ ፖኒ ከደቡብ ሱዳኗ ጆንግሌይ ግዛት ቦር ያደረሰችንን የዚህን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።