ባይደን የሩሲያን ሀብቶች ማገድና እና ቻይናንን የመገደብ እቅዳቸውን ገፍተውበታል

Your browser doesn’t support HTML5

በዚህ ሳምንት በተካሄደው የቡድን ሰባት ሀገሮች ስብሰባ ላይ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በመታገዳቸው ከማይንቀሳቀሱ የሩሲያ ንብረቶች የሚገኘውን ወለድ በመጠቀም፣ የዩክሬንን ጦርነት ማገዝ የሚያስችል ስምምነት ይፈልጋሉ። እንደ መሠረተ ልማት ፈንድ፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና ገበያውን አጥለቅልቀዋል ስለተባሉ የቻይና አረንጓዴ ቴክኖሎጂዎች የመሳሰሉ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ፣ ህብረት እንዲኖር ግፊት ያደርጋሉ።

ይሁን እንጂ ወደ ቀኝ እያዘነበለ ያለው የአውሮፓ የፖለቲካ ምህዳር እቅዶቹን ሊያወሳስበው ይችላል፡፡ ፓትሲ ውዳክስዋራ ተከታዩን ዘግባለች፡፡ ደረጀ ደስታ ወደ አማርኛ መልሶታል፡፡