በሰባት “አይቪ ሊግ” ትምህርት ቤቶች ተቀባይነት ያገኘው ኢትዮጵያዊ-አሜሪካዊ አዳጊ

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያዊ-አሜሪካዊው አዳጊ ወጣት፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአስደናቂ ውጤት በማጠናቀቅ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ክብር በሚሰጣቸው ሰባት “አይቪ ሊግ” ትምህርት ቤቶች ተቀባይነት አግኝቷል። በመጪው የትምህርት ዘመን፣ በሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርቱን የሚጀምረው ኤታን ፍጹም ርስቱ፣ ‘ኤስኤቲ' በተሰኘው የተማሪዎች የቀለም ትምህርት የብቃት ፈተና፣ 1ሺሕ600 በማምጣት የመጨረሻውን ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል፡፡

በዚህም፣ በዩናይትድ ስቴትስ በየዓመቱ ፈተናውን ከሚወስዱ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ተፈታኞች ውስጥ ከፍተኛውን ውጤት ከሚያስመዘግቡ አንድ ከመቶ ተማሪዎች ውስጥ ለመኾን ችሏል።