በኢታንግ ልዩ ወረዳ ግጭት 11 ሰዎች ሲገደሉ በሺሕዎች መፈናቀላቸው ተገለጸ

Your browser doesn’t support HTML5

በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ፣ ባለፈው እሑድ፣ በታጣቂዎች እና በመንግሥት የጸጥታ ኀይሎች መካከል በተከሠተ ግጭት 11 ሰዎች መገደላቸውን፣ የክልሉ የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጿል፡፡

በግጭቱ፣ ስምንት የልዩ ወረዳው ነዋሪዎች ሲገደሉ፣ ሦስት የመንግሥት የጸጥታ ኀይሎች ሕይወት ማለፉን የቢሮው ሓላፊ አቶ ባጓል ጆክ አስታውቀዋል፡፡

የተቃዋሚው የጋምቤላ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ፓርቲ በበኩሉ፣ በግጭቱ ከተገደሉት ሰዎች በተጨማሪ፣ ከ15ሺሕ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን አመልክቷል፡፡

የክልሉ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ቢሮ ደግሞ፣ በግጭቱ ምክንያት ከ10ሺሕ በላይ ሕዝብ ተፈናቅሏል፤ እገዛ ለማድረግም ርዳታ እያፈላለግን ነው፤ ብሏል፡፡