የካሜሩን የጦር ሠራዊት 300 የቦኮ ሐራም ታጋቾችን አስለቀቀ

Your browser doesn’t support HTML5

የካሜሩን የጦር ኃይል በናይጄሪያው ሽብርተኛ ቡድን በቦኮ ሐራም ቁጥጥር ሥር የነበሩ ከ300 በላይ ታጋቾች አስለቅቋል።

የጦር ኃይሉ ካሜሩንን ከናይጄሪያ እና ከቻድ ጋር በሚያዋስናት የድንበር አካባቢ "አልፋ" በሚል ስያሜ ባካሄደው አንድ ሳምንት የፈጀ ዘመቻ ብዛት ያላቸው የናይጄሪያው ቦኮ ሐራም ታጣቂዎችን መግደሉን አስታውቋል።

ያስለቀቃቸውን ታጋቾች በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል ወደሚገኝ የጦር ሠፈር ወስዶ ማስፈሩንም አመልክቷል። ሞኪ ኤድዊን ኪንድዜጋ ከያውንዴ ያስተላለፈው ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል።