ናይጄሪያ በ2023 ምርጫ የወንጀል ተከሳሾችን የፍርድ ሒደት ጀመረች

Your browser doesn’t support HTML5

ናይጄሪያ፣ በምርጫ ወቅት በተፈጸሙ ማጭበርበሮች ላይ መውሰድ በጀመረችው ርምጃ፣ የወንጀል ተከሳሾችን ፍርድ መመልከት ጀምራለች፡፡ ሒደቱ፣ ለአፍሪካ ዴሞክራሲ አዲስ የለውጥ ምዕራፍ እንደኾነ ተገልጿል።

እ.አ.አ በ2023 በተደረገው አጠቃላይ ምርጫ፣ ሁከት እና ብጥብጥ መነሣቱን ተከትሎ፣ አገሪቱ ሕግ በተላለፉት ላይ ክስ በመመሥረት የሕዝብ አመኔታን ለመመለስ ጥረት እያደረገች ነው።

ኤሜካ ጊብሰን ከአቡጃ ያደረሰንን ዘገባ፣ ስመኝሽ የቆየ ወደ አማርኛ መልሳዋለች።