ባይደን እና ትረምፕ በጥንቃቄ እና ግልጽ ባልሆነ አቋም የያዙት የማሪዋና ጉዳይ

Your browser doesn’t support HTML5

በፖለቲካ በተከፋፈለችው አሜሪካ የማሪዋና ጉዳይ ባልተለመደ መልኩ ብዙዎችን የሚያስማማ ጉዳይ ሆኗል። የሕዝብ አስተያየት ግምገማዎች እንደሚያሳዩት 88 ከመቶው አሜሪካዊያን ማሪዋና በከፊልም ቢሆን ሕጋዊ መሆን እንዳለበት ይስማማሉ።

ያም ቢሆን ሁለቱም የቀጣዩ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ተፎካካሪዎች ይህንን እየተቀየረ ያለ የአሜሪካውያን አመለካከት እየተጠቀሙበት እንዳልሆነ ካናቢስ የሚባሉት የሱስ አስያዥ መድሃኒቶች በሕግ እንዲፈቀዱ የሚሟገቱ ይናገራሉ።

የቪኦኤው ስካት ስተርንስ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።