በኢትዮጵያ የሙዚቃ አልበም ሥራዎች መሟሟቅ “የሙዚቃ ዘመን ለውጥን ያሳያል”

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ፣ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ዐዲስ የሙዚቃ አልበሞች በብዛት እየወጡ ነው፡፡ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ፣ ከስድስት በላይ አልበሞች ወደ አድማጮች ደርሰዋል፡፡

በቅርቡ የመጀመሪያ የሙዚቃ አልበሙን ያወጣው ድምፃዊ ማስተዋል እያዩ፣ በአድማጮች ዘንድ ያገኘው ተቀባይነት ለሁለተኛ ሥራው መነሣሣትን እንደፈጠረለት ይናገራል፡፡

የሙዚቃ አስተማሪ እና ድምፃዊት ብሌን ዮሴፍ በበኩሏ፣ በብዛት እየወጡ ያሉት የሙዚቃ አልበሞች፣ ልዩ ልዩ የዘፈን ቀለሞች ይዘው እንደመጡ ትገልጻለች፡፡ ይህም ከቀደሙት ዘመናት በተሻለ፣ የሙዚቃ አፍቃርያን አማርጠው እንዲሰሟቸው ዕድል ፈጥሯል፤ ትላለች፡፡