በቤጂንግ የግማሽ ማራቶን ላይ የተፈጠረውን ክስተት እንደሚያጣራ ፌዴሬሽኑ ገለፀ

Your browser doesn’t support HTML5

በቤጂንግ ግማሽ ማራቶኑ ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌት፣ ያለ አትሌቲክስ ፌደሬሽን እውቅና መሆኑን የፌዴሬሽኑ ጸሐፊ ተናግረዋል። ጸሐፊው አቶ ዮሐንስ እንግዳ፣ “አትሌቱ ፈቃድ ሳያገኝ የሄደ ቢሆንም ከተለያየ ቦታ ጥያቄ እየመጣ ስለሆነ እናጣራለን” ብለዋል፡፡

በእሁዱ ውድድሩ የተሳተፉ ሦስት አፍሪካውያን አትሌቶች፣ ሆን ብለው ቻይናዊ አትሌት እንዲያሸንፍ አድርገዋል መባሉን ተከትሎ፣ ከዚህ በኋላ ቁጥጥሮችን እንደሚያጠናክር የቻይና አትሌቲክስ ማኅበር አስታውቋል።