በጃዊ ወረዳ ግጭት ሲቪሎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለፁ

Your browser doesn’t support HTML5

በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጃዊ ወረዳ፣ ከትላንት በስቲያ ሰኞ ጀምሮ በመንግሥት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ዳግም በተቀሰቀሰው ግጭት፣ ሲቪሎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለፁ። ስማቸውን በይፋ እንዳንጠቅስ የጠየቁን የጃዊ ከተማ ነዋሪዎች፣ ዛሬም በከተማው እየተሰማ ባለው የተኩስ ድምፅ የተነሣ ከቤት መውጣት እንዳልቻሉ ገልጸው፣ ካለፈው ሰኞ ጀምሮ ከእንቅስቃሴ ተቆጥበው እንደሚገኙ አመልክተዋል። ከአካባቢው ባለሥልጣናትና ከሆስፒታል ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።