ባይደን ከጦርነት እስከ ኢኮኖሚ የሚዳስስሰውን ንግግራቸውን ዛሬ ምሽት ያደርጋሉ

  • ቪኦኤ ዜና

Your browser doesn’t support HTML5

ዩናይትድ ስቴትስ ለምርጫ እየተዘጋጀች ባለችበት ወቅት 'ስቴት ኦፍ ዩኒየን' የተሰኘውን የአሜሪካንን የዛሬ ሁኔታ የሚዳስስ ዓመታዊ ንግግራቸውን ዛሬ ያደርጋሉ።

ባይደን፣ ስለ ኢኮኖሚ አያያዛቸው፣ የሥነ-ተዋልዶ መብት፣ ሥደት እና በዩክሬን እና በጋዛ ስለሚካሄደው ጦርነት ያነሳሉ ተብሎ ይጠበቃል። የ81-ዓመቱ ባይደን፣ ንግግሩን ለሁለተኛ የሥልጣን ዘመን በአካል እና በአይምሮ ብቁ መሆናቸውንም ለማሳየት ይጠቀሙበታል ተብሏል። የአሜሪካ ድምፅ የዋይት ኃውስ ዘጋቢ አኒታ ፓውል ከዋሽንግተን ዲሲ ያደረሰችንን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።