ኢትዮጵያውያን አንድነታቸውን እንዲያድሱ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ጠየቁ

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያውያን አንድነታቸውን እንዲያድሱ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ጠየቁ

የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ሣኅለ ወርቅ ዘውዴ ከአራት ዓመታት በኋላ በአድዋ ከተማ ላይ በተከበረው 128 ዓመት የዓድዋ በመታሰቢያ በዓል ላይ "አንድነታችን እናድስ ከታሪካችን ጋራ እንታረቅ" ሲሉ ጥሪ አቀረቡ።

አባቶች ታሪክ በሠሩበት ተራርሮች ላይ ልጆቻቸው የእርስ በእርስ መገዳደል ታሪክ እንዳኖሩበት በቁጭት የተናገሩት ፕሬዚዳንቷ፣ በአሁኑ ጊዜም በአማራ ክልል የአንድ አገር ልጆች “እርስ በእስር እየተገዳደሉ ናቸው” ሲሉ ለሰላም ቅድሚያ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል።

በኦሮሚያ ክልልም “መሞት የሌላበች ንፁሃን እየሞቱ ነው” ብለዋል። የግጭቶች መቋጫ ውይይት እና ድርድር መኾኑን አስታውሰው ከእልቂት በፊት ችግሮች አስቀድሞ መፈታት እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።