በአሜሪካ የሰነድ አልባ ኢትዮጵያውያንን ውጣ ውረድ እንዴት መቀነስ ይቻላል?

Your browser doesn’t support HTML5

ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ፣ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰነድ አልባ ስደተኞች እንደሚኖሩ፣ የቅርብ ዓመታት መዛግብት ያሳያሉ። እኒኽ ስደተኞች፣ በአገሪቱ መደበኛ አስተዳደር ዕውቅና ስለሌላቸው፣ መሠረታዊ አገልግሎቶችን አለማግኘትን ጨምሮ ለበርካታ ሥነ ልቡናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ሲጋለጡ ይታያል። ዩናይትድ ስቴትስን የተስፋ ምድራቸው አድርገው ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች መካከል ጥቂት የማይባሉትም፣ ከሰነድ አልባነት በሚመነጩ ችግሮች መፈተናቸው አልቀረም።

ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ፣ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰነድ አልባ ስደተኞች እንደሚኖሩ፣ የቅርብ ዓመታት መዛግብት ያሳያሉ።

እኒኽ ስደተኞች፣ በአገሪቱ መደበኛ አስተዳደር ዕውቅና ስለሌላቸው፣ መሠረታዊ አገልግሎቶችን አለማግኘትን ጨምሮ ለበርካታ ሥነ ልቡናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ሲጋለጡ ይታያል። ዩናይትድ ስቴትስን የተስፋ ምድራቸው አድርገው ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች መካከል ጥቂት የማይባሉትም፣ ከሰነድ አልባነት በሚመነጩ ችግሮች መፈተናቸው አልቀረም። በዚህ ዙሪያ የተሰናዳውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።