የሱዳን ግጭት በኢትዮጵያ የኃይል ሽያጭ ላይ ጫና መፍጠሩ ተጠቆመ

Your browser doesn’t support HTML5

የሱዳኑ የእርስ በርስ ጦርነት፣ ኢትዮጵያ ለዚያች ሀገር በምታቀርበው የኤሌክትሪክ ኀይል መጠን ላይ ተጽእኖ ማሳደሩን፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኀይል አስታወቀ፡

የተቋሙ የኮምዩኒኬሽን ዲሬክተር አቶ ሞገስ መኰንን ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለመጠይቅ፣ በግጭቱ ምክንያት ሱዳን ለተጠቀመችበት የኤሌክትሪክ ኀይል፣ ከ70 ሚሊዮን ዶላር በላይ የአገልግሎት ክፍያ እንዳልፈጸመች ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም፣ በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያው መንፈቅ፣ ኢትዮጵያ ለሱዳን ለማቅረብ ካቀደችው የኤሌክትሪክ ኀይል መጠን ውስጥ፣ በሱዳኑ የውስጥ ግጭት የተነሣ ለመላክ የተቻለው 68 ከመቶ ብቻ እንደኾነ፣ የኮምዩኒኬሽን ዲሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።