መንግሥት ለታጣቂ ኀይሎች “ሐቀኛ የሰላም ጥሪ ያቅርብ” ሲል ኢዜማ ጠየቀ

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ የትጥቅ ግጭቶችን ለማስቆም፣ መንግሥት ለታጣቂ ኀይሎች ሐቀኛ እና ይፋዊ የሰላም ጥሪ እንዲያቀርብ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ(ኢዜማ) ፓርቲ፣ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ጠየቀ። የኢትዮጵያ መንግሥት ለትግራዩ የረኀብ አደጋ ትኩረት አልሰጠውም፤ በማለትም ፓርቲው ክስ አሰምቷል። በፓርቲው መግለጫ ላይ ከኢትዮጵያ መንግሥት ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ፡፡