የኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ ስምምነት በቀጠናው የፈጠረው ውጥረት ወዴት ያመራል?

Your browser doesn’t support HTML5

የአፍሪካ ህብረት የፀጥታው ምክርቤት በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል የተፈጠረውን ውጥረት በተመለከተ ባካሄደው ስበሰባ፣ ሁለቱ ሀገራት ጉዳዩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ትርጉም ያለው ውይይት እንዲያደርጉ መጠየቁን ሶማሊያ ተቃውማለች። ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ጋር በቅርቡ የፈረመችውን የመግባቢያ ሰነድ ቀድማ ካልሰረዘች፣ ለድርድር እንደማትቀርብም አስታውቃለች፡፡ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተካረረው ውጥረት ወዴት ያመራ ይሆን?