“የሰሜን ጎንደር ነዋሪዎች በድርቁ ምክንያት ወደ ከተሞች እየተሰደዱ ነው”- ዩኤንኦቻ

Your browser doesn’t support HTML5

በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን፣ ጃናሞራና ጠለምት ወረዳዎች በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ከአራት ሺ በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ከቀያቸውን ለቀው ወደ ከተሞች መሰደዳቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (UN-OCHA) ትናንት ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።

በሁለቱ ወረዳዎች በተከሰተው ድርቅ ከ86 ሺ በላይ የቤት እንስሳት መሞታቸውን እና ከ173 ሺህ በላይ መሰደዳቸውን ሪፖርቱ አመልክቷል።

የጃን አሞራ ወረዳ ግብርና ፅ/ ቤት በበኩሉ፣ በሶስት ወራት ውስጥ ብቻ 1ሺ 4 መቶ ሰዎች ቤታቸውን ለቀው ወደ ከተሞች መሰደዳቸውን ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ አረጋግጠዋል።