ለከፍተኛ ትምህርት የሚያበቁ ክህሎቶችን የሚያስተምረው "ትጋት-ለስኬት"

Your browser doesn’t support HTML5

“ቻቺ ታደሰ”፥ በኢትዮጵያ የሙዚቃ ትዕይንት ውስጥ ዕውቅ ከኾኑ ድምፃውያን መካከል አንዷ ናት። ከሙዚቃው ባሻገርም በምትሳተፍባቸው ማኅበረሰብ አገዝ እንቅስቃሴዎች የምትታወቀው ቻቺ፣ በቅርቡ በትምህርት መስክ፣ ወጣት ኢትዮጵያንን ለማገዝ አንድ መርሐ ግብር ይፋ አድርጋለች። የመርሐ ግብሩ መጠሪያ “soar to success” ይባላል። እኛም ተማሪዎችን፣ በተለይ ለዓለም አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት ስለሚያዘጋጀው ተቋም የተወሰኑ ጥያቄዎች አቅርበንላታል።