የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሥራ በጥናት ላይ እንዲመሠረት ተጠየቀ

Your browser doesn’t support HTML5

ሀገራዊ የሰላም ግንባታ የእንቅስቃሴ ማዕከል፣ መንግሥታዊ ካልኾኑ ድርጅቶች ወደ ኅብረተሰቡ ተዛውሮ በማኅበራዊ ንቅናቄ መልክ መመራት እንዳለበት ተጠቆመ፡፡

በነባር ሀገራዊ ተቋሞች ዕሴቶች እና ተሞክሮዎች ላይ የተመሠረተ ማኅበራዊ ንቅናቄም፣ የሰላም ግንባታ ሒደቱን እንደሚጠናክረው ተመልክቷል፡፡

በዘመናችን፣ በሥራ ላይ የሚገኙት የግጭት መፍቻ ዘዴዎች፣ ከወቅቱ ችግሮች አኳያ በቂ እንዳልኾኑና ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዐዲስ ስልቶች እንደሚጠበቁ ተገልጿል፡፡

ድርጅቶቹ፣ የሰላም ግንባታ መድረኮችን በማዘጋጀት፣ ተፋላሚ ኃይሎችን ለውይይት እንዲያተጓቸውም ጥሪ ቀርቧል፡፡