በዐዲስ አበባ የጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች ማትጊያ ማዕከል በርካቶችን እያበቃ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

በዐዲስ አበባ፣ በመንግሥት እና በግሉ ዘርፍ ትብብር ከሁለት ዓመት በፊት የተቋቋመው “ክርኤቲቭ ሃብ”፣ የወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ማትጊያ ማዕከል ሲኾን፣ ጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎችን ይደግፋል፡፡

የተቋሙ ሥራ አስኪያጅ አቤኔዘር ሰይፈ እንደገለጸው፣ “ክርኤቲቭ ሃብ” የሥራ ፈጠራ ሐሳብ ያላቸውን ወጣቶች በአባልነት ይቀበላል፡፡ ከዚያም፣ የተለያዩ ሥልጠናዎችን በመስጠት እና ሐሳቦቻቸውን ወደ ተግባር የሚለውጡበት ቦታ እና ቤተ ሙከራ በማዘጋጀት ያግዛቸዋል፡፡

የማዕከሉ ተጠቃሚዎችም፣ በማዕከሉ ድጋፍ ሐሳቦቻቸውን ወደ ተግባር ለመቀየር እና ሥራዎቻቸውንም ለማስፋፋት እንደቻሉ ይናገራሉ፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።