በትግራይ አራት አመራሮች ከሓላፊነት የተነሡት “ሥራን ለመፈጸም ባለመቻል” እንደኾነ ክልሉ ገለጸ

Your browser doesn’t support HTML5

በትግራይ አራት አመራሮች ከሓላፊነት የተነሡት “ሥራን ለመፈጸም ባለመቻል” እንደኾነ ክልሉ ገለጸ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የክልሉን አራት ከፍተኛ አመራሮች ከሓላፊነታቸው አነሡ፡፡

የክልሉ የኮምዩኒኬሽን ጽሕፈት ሓላፊ አቶ ረዳኢ ሓለፎም፣ ርምጃው፥ ከአመራሮቹ የሥራ አፈጻጸም ጋራ የተያያዘ እንደኾነ ገልጸዋል፡፡

አቶ ረዳኢ፣ “መንግሥት የሥራ ሓላፊዎችን ይመድባል እንዲሁም የመንግሥትን ሥራ መፈጸም ያልቻሉትን ያነሣል፤” ሲሉ፣ ስለተወሰደው ርምጃ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡ ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።