በስፔን የአገር አቋራጭ እና የማራቶን ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያዊቷ ልቅና አምባው፣ በስፔን የዓለም አትሌቲክስ አገር አቋራጭ ውድድር ስታሸንፍ፤ በቫሌንሺያ ግማሽ ማራቶን ደግሞ፣ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የብር እና የነሐስ ሜዳልያ አሸንፈዋል፡፡

በእንግሊዝ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ እና በማንቸስተር ዩናይትድ አንጋፋው ተጫዋች ሰር ቦቢ ቻርልተንን ሞት፣ በርካታ የስፖርቱ ዓለም ሰዎች ኀዘናቸውን እየገለጹ ነው፡፡

የእስራኤል - ሐማስ ጦርነት፣ በስፖርቱ ላይ እያሳደረ ያለው ተጽእኖ ሲቀጥል፤ አልጄሪያ፥ የፍልስጥኤም ብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎችን አስተናግዳለኹ፤ ብላለች፡፡

አሜሪካዊው ቤን ሼልተን፣ በጃፓን ኦፕን፣ ሩሲያዊ ተጋጣሚውን በማሸነፍ፣ የመጀመሪያውን የ“ ATP” ዋንጫውን አንሥቷል፡፡