ለሐማስ ጥቃት ሰለባዎች በኢትዮጵያ የእስራኤል ኤምባሲ የመታሰቢያ ሥነ ሥርዐት ተካሔደ

Your browser doesn’t support HTML5

በኤምባሲው የመታሰቢያ ዝግጅት ላይ፣ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካዮች፣ ቤተ እስራኤላውያንና ልዩ ልዩ ተጋባዦች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካይ አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን፣ “በተፈጠረው አሠቃቂ አደጋ የተሰማንን ጥልቅ ኀዘን እገልጻለኹ፤” ብለዋል፡፡ እስራኤል እና ኢትዮጵያ፣ መንፈሳዊ ትስስር እንዳላቸው የጠቀሱት አምባሳደሩ፣ “የደረሰው ኀዘን የኹላችንም ነው፤” ሲሉም አክለዋል፡፡

አስተያየታቸውን የሰጡን ቤተ እስራኤላውያንም፣ በሃይማኖታዊ በዓል ወቅት በተፈጸመው ድንገተኛ የሐማስ ጥቃት የደረሰው ሞት እና ጉዳት እጅግ እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለልኝ አድማሱ፣ ኀዘናቸውን የገለጹ አካላትን አመስግነዋል፡፡