ቡዳፔስት የሚገኘው የኢትዮጵያ ቡድን ለመጨረሻዎቹ ውድድሮች እየተዘጋጀ ነው

  • ቪኦኤ ዜና

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን፣ በቡዳፔስቱ 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ እያስገኘ ባለው ብቃት እና ውጤት፣ አዎንታዊ አስተያየቶችን እያገኘ ነው።

ቀሪዎቹ ውድድሮች፣ ነገ እና ከነገ በስቲያ ይቀጥላሉ፡፡ ሻምፒዮናው፣ በሴቶች እና በወንዶች ማራቶን፣ በወንዶች እና በሴቶች የ5000 ሜትር፣ እንዲሁም በሴቶች የ3000 ሜትር መሰናክል ውድድሮች እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።

ዘጋቢያችን ኤቢሳ ነገሰ፣ በቡዳፔስት የአትሌቶች የልምምድ ጣቢያ ተገኝቶ፣ የ3000 መሰናክል ውድድር ተሳታፊ አትሌቶችንና አሠልጣኞችን አነጋግሯል። ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።