ዩናይትድ ስቴትስን ተስፋ ያደረጉ ፍልሰተኞች በሺሕዎች የረገፉበት “ብሩክስ ካውንቲ”

  • ቪኦኤ ዜና

Your browser doesn’t support HTML5

ዩናይትድ ስቴትስን ተስፋ ያደረጉ ፍልሰተኞች በሺሕዎች የረገፉበት “ብሩክስ ካውንቲ”

የዩናይትድ ስቴትስ የድንበር ቁጥጥር መሥሪያ ቤት መዝገብ እንዳሰፈረው፣ እ.አ.አ. ከ1998 ዓ.ም. ወዲህ፣ በዩናይትድ ስቴትስ እና በሜክሲኮ ድንበር ወሰን ላይ፣ ቁጥራቸው ከስምንት ሺሕ የሚበልጡ ፍልሰተኞች ሞተዋል።

ድንበሩን ለማቋረጥ የሚሞክሩ ፍልሰተኞችን፣ በዚኽን ያህል ቁጥር ለሞት የዳረጋቸው፣ “ብሩክስ ካውንቲ” በተባለው የደቡባዊ ቴክሳስ ወረዳ ያለው፣ ከባድ ሙቀት እና እጅግ አስቸጋሪ የመሬት አቀማመጥ ነው።

የአሜሪካ ድምፅ የኢሚግሬሽን ጉዳዮች ዘጋቢ አሊኒ ባሮስ፣ “የፍጅት ሜዳዎች” በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀውን አካባቢ ጎብኝታ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።