እየጠነከረ ያለው ድርቅ ሴቶችን በበለጠ እየጎዳ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

ከፍተኛ ተለዋዋጭ የአየር ሁኔታ፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ለውጡ የሚያስከትላቸው እንደ ድርቅ የመሳሰሉ አደጋዎች ባልተመጣጠነ ሁኔታ ሴቶች ላይ ተፅእኖ እንደሚያደርሱ በርካታ ጥናቶች ያሳያሉ። በ60 ዓመታት ውስጥ ያልታየው ድርቅ በተከሰተባቸው የአፍሪካ ቀንድ ሀገሮች የሚኖሩ ሴቶችም በባህላዊ ልማዶችና ያልተመጣጠነ የሀብትና የሥልጣን ክፍፍል ምክንያት ድርቁ ከወንዶች በበለጠ ለስቃይ ዳርጓቸዋል።