የምስራቅ ወለጋ አኖ ከተማ ነዋሪዎች ሰለ ሠላም ይናገራሉ

Your browser doesn’t support HTML5

በኦሮምያ ክልል፣ ምስራቅ ወለጋ ዞን፣ አኖ ከተማ ባለፈው ሳምንት ጥር 25/2015 ዓ.ም በታጣቂዎች ተፈጸመ በተባለው ጥቃት 60 ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውን የዐይን እማኞችና የተጎጂ ቤተሰቦች ተናግረዋል። ጥቃቱን ተከትሎ በከተማው ውስጥ ውጥረት መንገሱንና ነዋሪዎች ሥጋት ውስጥ መግባታቸውን ወደ ስፍራው አቅንቶ የነበረው የአምቦው ዘጋቢያችን ከስፍራው ያጠናቀረውን ማሰማታችን ይታወሳል።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት ታጣቂዎች በሚፈጽሙት ጥቃት እና በነዋሪው ህዝብ ደህንነት ላይ በቀኑት ስጋት ሳቢያ የነበራቸው ማኅበራዊ መስተጋብር መላላቱን፣ የኑሮ ሁኔታ መክበዱንና ወጥቶ መግባትም ሥጋት መሆኑን ነዋሪዎቹ ይናገራሉ።

የፀጥታ ችግር የደቀነውን ፈተና እና በአካባቢው ሰላም ይሰፍን ዘንድ መደረግ አለበት የሚሉትን ጨምሮ ናኮር የከተማይቱ ነዋሪ ከሆኑ የአማራ እና የኦሮሞ ተወላጆች ጋር ያደረገውን ውይይት ይዞ ቀርቧል።