በባህር ዳር የምልክት ቋንቋ አስተርጓሚዎች እጥረት ገጥሟል

Your browser doesn’t support HTML5

በምልክት ቋንቋ የሠለጠኑ አስተርጓሚዎች በበቂ ሁኔታ ባለመኖራቸው የማኅበራዊ አገልግሎት ለማግኘት መቸገራቸውን መስማት የተሳናቸው የባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ ። በማኅበር የተደራጁት መስማት የተሳናቸው ነዋሪዎች ወደ ፍትኅ፣ የህክምናና ሌሎች የማኅበራዊ አገልግሎት ተቋማት ሲሄዱ አስተርጓሚ በማጣት መቸገራቸውን በመግለጽ መንግሥት በየአገልግሎት ሰጭ ተቋማቱ አስተርጓሚ እንዲመደብ ጠይቀዋል። /ሙሉውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/