በርካታ ፍልሰተኞች ዩናይትድ ስቴትስ ደቡብ ድንበር እየደረሱ ነው
Your browser doesn’t support HTML5
በቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕ አስተዳደር የወጣውና ፍልሰተኞች ድንበር ላይ ተይዘው እንዲመለሱ የሚያዘው ፖሊሲ በመጪው ረቡዕ ያበቃል፡፡ በዚህ የተነሳም ከፍተኛ ቁጥር ያላችው ፍልሰተኞች በዩናይትድ ስቴትስ ደቡብ ድንበር በኩል በመድረስ ላይ ናቸው። በሺህ የሚቆጠሩ ፍልሰተኞች ሜክሲኮ ድንበር ላይ በምትገኘው ሲዩዳድ ኋሬዝ ከተማ በመሰባሰብ ወደ አሜሪካ ለመዝለቅ በዝግጅት ላይ መሆናቸው ተዘግቧል፡፡