በዩጋንዳ የተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ እየቀነሰ ነው ተባለ

Your browser doesn’t support HTML5

የዩጋንዳ የጤና ሚኒስቴር በሃገሪቱ የተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ስርጭቱ ጋብ ያለ መሆኑን በማስታወቅ ላይ ይገኛል።

የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ይህን መግለጫ ያወጣው፣ የአገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን አፍትልኮ የወጣ ነው የተባለ አንድ ሰነድ በመጥቀስ ወረርሽኙ እስከ ሚቀጥለው ሚያዚያ ወር ድረስ የ500 ሰዎችን ሕይወት ሊነጥቅ እንደሚችል መዘገባቸውን ተከትሎ ነው።

ወረርሽኙ መታየት ከጀመረበት ከመስከረም ወር አንስቶ እስከአሁን 137 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ሲታወቅ፣ ሌሎች 54 ሰዎች ደግሞ ሕይወታቸውን አጥተዋል።

/ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ/