በኢትዮጵያ ዘጋቢ ፊልሞች ለምን በብዛት አይሰሩም?

Your browser doesn’t support HTML5

ላለፉት 50 አመታት ዓለም አቀፍ ብቃት ያላቸው ዘጋቢ ፊልሞችን ለሰሩ ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጠው 'ኤሚ' አዋርድ፣ ለኢትዮጵያዊ ባለሙያዎች ባለፈው አመት ሽልማት የሰጠው ለመጀመሪያ ግዜ ነው። ጋዜጠኛ ሀድራ አህመድ እና የካሜራ ባለሙያው ንጉሱ ስለሞን ሽልማቱን ያገኙት ኤቢሲ የአሜሪካ ቴሌቭዥን ጣቢያ ከሶስት አመት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ በተከሰከሰው ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን ዙሪያ በሰራው ዘጋቢ ፊልም በነበራቸው ተሳትፎ ነው።