በሰሜኑ ጦርነት ሳቢያ የተቋረጠው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሊመለስ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተያያዘ ከአንድ ዓመት በላይ ያለ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቆዩ የአማራ፣ የአፋርና የትግራይ አንዳንድ አካባቢዎች በቀናት ውስጥ አገልግሎቱን እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ኤሌክሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡

ባለፈው ነሐሴ እንደገና የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ የመከላከያ ኃይሉ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ሰብአዊ ድጋፍ እንዲዳረስና መሰረታዊ አገልግሎቶች አንዲጀምሩ እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ መንግሥት እየገለጸ ይገኛል።