”በጋምቤላ በጎርፍ ሳቢያ የተፈናቀሉ ሰዎች አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ናቸው” ዩ ኤን ኦቻ

Your browser doesn’t support HTML5

በጋምቤላ ክልል በጎርፍ ምክንያት የተፈናቀሉ ሰዎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አስታውቋል ። እየተደረገላቸው ያለው ድጋፍም ተመጣጣኝ አይደለም ብሏል። ካለፈው አመት ነሐሴ ጀምሮ እስከአሁኑ ጥቅምት ወር የጣለው ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ በጋምቤላ ክልል ከሚገኙ 12 ወረዳዎች ውስጥ ከ185 ሺ በላይ የሚሆኑ ሰዎች መፈናቀላቸውንም ጽ/ቤቱ ትናንት ባወጣው ሪፖርት አመልክቷል።

በጋምቤላ ክልል በጎርፍ ምክንያት የተፈናቀሉ ሰዎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥእንደሚገኙ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አስታውቋል ።

እየተደረገላቸው ያለው ድጋፍም ተመጣጣኝ አይደለም ብሏል።
ካለፈው አመት ነሐሴ ጀምሮ እስከአሁኑ ጥቅምት ወር የጣለው ዝናብባስከተለው ጎርፍ በጋምቤላ ክልል ከሚገኙ 12 ወረዳዎች ውስጥ ከ185 ሺ በላይየሚሆኑ ሰዎች መፈናቀላቸውንም ጽ/ቤቱ ትናንት ባወጣው ሪፖርትአመልክቷል።

የጋምቤላ ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽህፈት ቤት በበኩሉ ተፈናቃዮችወደየአካባቢያቸው እየተመለሱ ነው ብሏል።

የተመለሱትን ሰዎች ቁጥር ግን አልጠቀሰም።